የባለስልጣኑ የሶስተኛ ዙር የሰንዳፋ የአካል ብቃትና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሂደት የመስክ ምልከታ ተደረገ
የባለስልጣኑ የሶስተኛ ዙር የሰንዳፋ የአካል ብቃትና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና ሂደት የመስክ ምልከታ ተደረገ
02/04/2018 ዓ.ም
** ሰንዳፋ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩንቨርሲቲ ሰንዳፋ ካምፓስ ነባር ፖራ- ሚሊተሪ ኦፊሰሮች እየተሰጠ ያለው የአካል ብቃትና የንድፈሀሳብ ስልጠና የባለስልጣኑ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ፣ የስልጠናው አስተባባሪዎች እና የዩንቨርስቲው አመራሮች የስልጠናው ሂደት ምልከታና ጉብኝት አድርገዋል።
በስልጠናው የተግባቦት ጥበብ ፣ ሀገር ወዳድነት፣የሰብዓዊ መብት አያያዝ፣የሃይል አጠቃቀም፣ አገልግሎት አሰጣጥ እና የአካል ብቃት ስልጠና በእቅዱ መሰረት በተገቢው መንገድ እየተከታተሉ መሆናቸውን በምልከታው ለማረጋገጥ ተችሏል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments