ባለስልጣኑ "18ተኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን በድምቀት አከበረ።
ባለስልጣኑ "18ተኛውን የሠንደቅ ዓላማ ቀን በድምቀት አከበረ።
03/02/2018 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን "ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ሉአላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ" በሚል መሪ ቃል 18ተኛውን ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀንን የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች፣ ኦፊሰሮችና መላሙ የተቋሙ ሰራተኞች በተገኙበት አከበረ።
ክብረ-በዓሉ በብሄራዊ ህዝብ መዝሙር የተጀመረ ሲሆን የባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ የዘንድሮውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን የህዳሴ ግድብ እና ለሎች በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ወደ ስራ በገቡበት ወቅትና እንዲሁም ተቋማችን ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።
ኃላፊው አያይዘውም ሰንደቅ ዓላማችን የክብራችንና የሉአላዊነት መገለጫ አርማችን እንደመሆኑ መጠን ይህንን ቀን ስናከብር አባቶቻችን በደም ጠብቀው ያቆዩልንን ሀገር በስኬት የማንሰራራትና የከፍታ ዘመን የምናስቀጥልበትና በቁርጠኝነት የምንሰራበት ሊሆን እንደሚገባ በአፅንኦት ገልጸዋል።
ዘገባው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ነው።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments