በአዋኪ ድርጊቶች እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ዙሪያ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሄደ
በአዋኪ ድርጊቶች እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ዙሪያ የህዝብ ውይይት መድረክ ተካሄደ
30/01/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በኮልፌ ፣ በአራዳ እና በቦሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በአዋኪ ድርጊቶችን መከላከል ላይ፣ በደንብ ቁጥር 150/2015 እና በፀረ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ዙሪያ በህዝብ ንቅናቄ መድረክ በማዘጋጀት ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር ተፈጥሯል ::
በግንዛቤ መድረኮቹ አዋኪ ድርጊቶችን መከላከል እና በስነምግባር እና ብልሹ አሰራር መከላከል በሚል ርዕስ ለህብረተሰቡ የተዘጋጀ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ።
በመድረኩ ከአዋኪ ድርጊት ጋር በተያያዘ በተለያዩ መንገዶች ግንዛቤ ተፈጥሯል በተለይም ደግሞ በት/ቤቶች ላይ ለተማሪዎች በቅ/መከላከል ባለሙያዎቻችን አማካኝነት በየጊዜው ግንዛቤ የመፍጠር ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል ።
ህብረተሰቡ በአሁኑ ሰዓት ህገ ወጥነትን ለመከላከል እያደረገ ያለውን ስራ በማጠናከርና ተባባሪ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባና ከመሰል አዋኪ ተግባራት ልጆቻቸውና ራሳቸውን በማራቅ ለሌሎች አርዓያ መሆን እንደሚገባቸው በመድረኮቹ ተገልጿል ።
የደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ደንቡና መመሪያውን ተፈፃሚ እንዲሆን እና በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ በማድረግ ለብልሹ አሰራር እና ፀረ ሙስና ተጋላጭነት መቆጣጠር መቻል ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ ተገልጿል::
በመድረኩ አዋኪ ድርጊትን በመከላከል ህብረተሰቡም ከደንብ ማስከበር ጋር በመቀናጀት የግንዛቤ ስራዎችን አጠናክረው መስራትና እርምጃ እንዲወሰድ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንዳለባቸው ተነግሯል ።
ወጣቱን ከአዋኪ ድርጊቶችን እና ብልሹ አሰራሮችን እንዴት እራሱን መከላከልና መቆጣጠር እንደሚቻል በሰነዱ በዝርዝር ተገልፃል ።
በመጨረሻም ከተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች በተሰጡ ሀሳብ አስተያየት ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ ከመድረኩ ለተነሱት ሀሳብና አስተያየት ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments