
ባለስልጣኑ እሬቻ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ወደስራ መግባቱ አስታወቀ
ባለስልጣኑ እሬቻ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ ወደስራ መግባቱ አስታወቀ
22/ዐ1/2018 ዓ.ም
** አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የእሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበርና እንግዶች ለመቀበል እና በዓሉን ለማክበር የቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታወቀ።
ለበዓሉ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን በዓሉ በሚከበርበት ቦታ የጸጥታ ችግር እንዳይፈጠር የተቋሙ አመራሮችና ኦፊሰሮች የተሰጣቸውን ኃላፊነትና ስምሪት በቁርጠኝነት ለመወጣት ዝግጁ በማድረግ ለእንግዶች ምቹነትና ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር አስፈላጊ አገልግሎቶች ለመስጠት መዘጋጀቱ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments