በህብረት ችለናል ! ባለስልጣኑ የህዳሴ ግድብ...

image description
- In code inforcement    0

በህብረት ችለናል ! ባለስልጣኑ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ የፓነል ውይይት መድረክ አካሄደ

በህብረት ችለናል !

ባለስልጣኑ የህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ የፓነል ውይይት መድረክ አካሄደ

                 05-ዐ1 -2018 ዓ.ም
                 **አዲስ አበባ**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን " የህዳሴ ግድባችን የኢትዮጵያ ማንሰራራት ነው " በሚል መሪ ቃል የህዳሴ ግድብ ምረቃ በተመለከተ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በወርቃማ ሰኞ ፕሮግራም ላይ ከመላው የማዕከል ሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ  ።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ-አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በትውልልድ ቅብብሎሽ የተገነባ ኢትዮጵያዊያን ታሪክ መስራት እንደሚችሉ ለዓለም ያሳዩበት ድንቅ ፕሮጀክት ነዉ ሲሉ ገልጸዋል ።

ህዳሴ ግድቡ  በርካታ ዲፕሎማሲያዊ ጫናዎችን በመቋቋም በራሳችን ባለሙያዎችና በራችሳችን ገንዘብ በመገንባት ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ሀያልነቷን ያሳየችበት መጭው ትውልድ የሚኮራበት ድል ነው ሲሉ ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል ።

ለመወያያ የተዘጋጀው ሰነድ በባለስልጣኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተስፋሁን አሉላ ቀርቧል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁን አስመልክቶ የግድቡ አንድምታዎችን ለሀገሪቱ ህዳሴ ፣ ለተፋሰሱ እና ቀጠናዊ ትስስር እንዲሁም ለአፍሪካ ትንሳኤ የሚኖረውን ሚና   ከሰራተኛው ጋር ውይይት  አድርጓል።

የግድቡ መጠናቀቅ ሀገራዊ መነቃቃትና ህዝባዊ ተሳትፎ ለሌሎችም ሀገራዊ ልማቶች የጋራ መግባባት በመፍጠር ማስቀጠል እንደሚገባ በሰነዱ ተገልጿል ።

በመድረኩ የተገኙት የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው መላው ኢትዮጽያዊን በአንድነት ተደጋግፈው የሰሩትን ዘመን ተሻጋሪ ሀገራዊ ፕሮጀክት የሆነውን  የታላቁ ህዳሴ ግድብ በመገንባት ማጠናቀቅ በመቻላችን እንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

በመጨረሻም በሰነዱ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት በማድረግ ለተነሱ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ከመድረኩ ምላሽና አስተያየት ተሰጥቶበት መድረኩ ተጠናቋል ።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments