
ባለስልጣኑ የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን የበከለ ግለሰብ 3 መቶ ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
ባለስልጣኑ የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን የበከለ ግለሰብ 3 መቶ ሺህ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
ሐምሌ 17/2017
****አዲስ አበባ****
የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 ልዩ ቦታው ጎርጎርዮስ አካባቢ የሚገኘው ክላሲክ ኮንሰልቲንግ እንጂነርስ ኃላፊነቱ የተረጋገጠ የግል ማህበር የሽንት ቤት ፍሳሽ በመልቀቅ አካባቢውን በመበከል ደንብ በመተላለፉ መቀጣቱ ተገለፀ።
ተቋሙ ከዚህ በፊት እንዲያስተካክል ግንዛቤ ቢሰጠውም ምንም አይነት የማስተካከያ እርምጃ ባለመውሰዱ በደንብ ቁጥር 180 /2017 መሰረት 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር መቀጣቱን የወረዳው ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ እስጢፋኖስ ገልፀዋል።
ባለስልጣን መረጃ በመስጠት ብክለት መከላከል እንዲቻል የጠቆሙትን የህብረተሰብ ክፍሎችን እያመሰገነ በቀጣይ ህብረተሰቡና ተቋማት ከዚህ ዓይነት ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል::
መረጃው:- የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments