ባለስልጣኑ በ2017 በጀት አመት ያከናወናቸው የ...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ በ2017 በጀት አመት ያከናወናቸው የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች ልምድ ሊወሰድባቸው የሚገባ መሆኑ ተገለፀ

ባለስልጣኑ በ2017 በጀት አመት ያከናወናቸው የመንግስትና የፓርቲ ስራዎች ልምድ ሊወሰድባቸው የሚገባ መሆኑ ተገለፀ

                 26/10/2017 ዓ.ም
                 ****አዲስ አበባ****

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በ2017 በጀት አመት በተከናወኑ የመንግስት እና ፓርቲ ተግባራት ላይ በከተማ አስተዳደሩ በተቋቋመ የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት የሰነድና የተግባር ምልከታ በማድረግ  ግብረ-መልስ ተሰጥቷል።

ሱፐርቪዥኑ ባለስልጣኑ ለተገልጋይ እና ለሰራተኛው ምቹ የስራ አካባቢ በመፍጠር ፣ የሚዲያና የህዝብ ግንኙነትና የተቋም ግንባታ ስራዎች በራስ አቅም ስቱዲዮ በመገንባት መሠራቱ ልምድ ሊወሰድባቸው የሚገባ መሆኑ የሱፐርቪዥኑ ቡድን ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ሽታዬ መሐመድ ገልፀዋል።

በመደበኛ ስራው  የግንዛቤ፣ የስልጠና ፣የተቋማት ቅንጅታዊ ስራዎች ና ህብረተሰቡ በማሳተፍ የተሰሩ የቁጥጥርና የእርምጃ አወሳሰድ ስራዎች እንደዚሁም የተደራጀ የፓርቲ መረጃዎች ተለይተውና ተሰንደው መቀመጣቸው በሱፐርቪዥን አባላት በጥንካሬ ተነስተዋል::

በመጨረሻም የባስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በእውቀት ላይ የተመሰረተ ሱፐርቪዥን ላደረገው የቡድን አባላት በማመስገን በቀጣይ የበለጠ በመስራት በከተማ አስተዳደሩ የተሰጣቸው ሀላፊነት በብቃት እንደሚወጡ ገልፀዋል ።

መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments