ባለስልጣኑ በብስክሌት መንገድ በመኪና የሄደችው...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ በብስክሌት መንገድ በመኪና የሄደችው ግለሰብ 100 ሺህ ብር መቀጣቱ አስታወቀ

ባለስልጣኑ በብስክሌት መንገድ በመኪና የሄደችው ግለሰብ 100 ሺህ ብር  መቀጣቱ አስታወቀ
      
           14/10/2017 ዓ.ም
          ****አዲስ አበባ****

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ሲኤምሲ ሚካኤል ቤተክርስቲያን  አካባቢ በልማት ኮሪደር በተሰራው በብስክሌት መንገድ ላይ መኪና በማሽከርከር ደንብ የተላለፈችው ግለሰብ ከለሚኩራ ክፍለ ከተማ ከሰላምና ጸጥታ አባላት እና ትራፊክ ማኔጅመንት አባላት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል መቅጣቱን አስታወቀ ።

አሽከርካሪዋ በቸልተኝነት ደንብ ተላልፋ የባለስልጣኑ ኦፊሰሮች ክትትልና በህብረተሰቡ ጥቆማ መሠረት  ግለሰቧ ከነተሽከርካሪዋ  በቁጥጥር ስር በማዋል 100.000 (አንድ መቶ ሺህ ብር ) ብር ተቀጥታለች ። 

ባለስልጣኑ ደንብ የሚተላለፉ  ድርጅቶች እና ግለሰቦች በህጉ መሠረት የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም  አስታውቋል ። 

ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች  መረጃ  በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ተቋሙ ጥሪውን ያቀርባል። 

መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments