በእግረኞች መንገድ በተሽከርካሪ የሄደው ግለሰብ...

image description
- In code inforcement    0

በእግረኞች መንገድ በተሽከርካሪ የሄደው ግለሰብ 100 ሺህ ብር መቀጣቱ ተገለፀ

በእግረኞች መንገድ በተሽከርካሪ የሄደው ግለሰብ 100 ሺህ ብር  መቀጣቱ ተገለፀ
      
           12/10/2017 ዓ.ም
          ****አዲስ አበባ****

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በትላንትናው እለት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በልማት ኮሪደር በተሰራው እግረኞች መንገድ ላይ በኮድ 4 ተሽከርካሪ መኪና በመሄድ ደንብ የተላለፈው  አሽከርካሪ ከፌደራል ፖሊስ ሲቲዝን ኢንጌጅመንት እና ከአዲስ አበባ ትራፊክ ፖሊስ  ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር በማዋል መቅጣቱን አስታወቀ ።

ተሽከርካሪው ንብረትነቱ የመንግስት የሆነ የአቃቂ ቃሊቲ ክፋለ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ-ፈቃድ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት የሚጠቀምበት ሲሆን በህብረተሰቡ ጥቆማ መሠረት ክትትል በማድረግ  ግለሰቡ ከነተሽከርካሪው  በቁጥጥር ስር በማዋል 100.000 (አንድ መቶ ሺህ ብር ) ብር ተቀጥቷል ። 

ባለስልጣኑ ደንብ የተላለፈው የመንግስት ይሁን የግል  ድርጅቶች እና ግለሰቦች ያለዩነት በህጉ መሠረት የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም  አስታውቋል ። 

ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች  መረጃ  በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ተቋሙ ጥሪውን ያቀርባል። 

መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments