የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የ...

image description
- In code inforcement    0

የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ጀመረ ።

የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ጀመረ ። 

               20 - 09 - 2017 ዓ.ም
                   **አዲስ አበባ**    

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ለማዕከል ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎች ፣ ባለሙያዎች እና የክ/ከተማ አስተባባሪዎችና ሲቪል ሰራተኞች ሁለተኛ ዙር ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል ። 

ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና በጊዜ አጠቃቀም ፣ውጤታማ የቡድን የትብብር ችሎታ እና የራስ ተነሳሺነት ወይም እራስን ማስተዳደር በሚሉ ርዕሶች ላይ የሚሰጥ ይሆናል ። 

እየተሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሰልጣኞቹ ላይ የአመለካከትና የዕውቀት ዕድገት እንደሚያመጣ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ገልጸዋል ።

ስልጠናው ለምንሰራው ስራ እና ለግል ህይወታችን ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ በንቃትና ትኩረት በመስጠት መከታተል እንደሚገባ አሳስበዋል። 

መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments