
የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ጀመረ ።
የባለስልጣኑ የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠት ጀመረ ።
20 - 09 - 2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን የስልጠናና ቅድመ መከላከል ዘርፍ ለማዕከል ዳይሬክተሮች ፣ ቡድን መሪዎች ፣ ባለሙያዎች እና የክ/ከተማ አስተባባሪዎችና ሲቪል ሰራተኞች ሁለተኛ ዙር ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀምሯል ።
ለሶስት ቀናት በሚቆየው ስልጠና በጊዜ አጠቃቀም ፣ውጤታማ የቡድን የትብብር ችሎታ እና የራስ ተነሳሺነት ወይም እራስን ማስተዳደር በሚሉ ርዕሶች ላይ የሚሰጥ ይሆናል ።
እየተሰጠ ያለው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሰልጣኞቹ ላይ የአመለካከትና የዕውቀት ዕድገት እንደሚያመጣ የባለስልጣኑ ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ገልጸዋል ።
ስልጠናው ለምንሰራው ስራ እና ለግል ህይወታችን ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ በንቃትና ትኩረት በመስጠት መከታተል እንደሚገባ አሳስበዋል።
መረጃው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ነው፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments