ባለስልጣኑ የደንብ ጥሰት የፈጸመውን የከተማ አብ...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ የደንብ ጥሰት የፈጸመውን የከተማ አብቶቢስ አሽከርካሪ መቅጣቱን አስታወቀ

ባለስልጣኑ የደንብ ጥሰት የፈጸመውን የከተማ አብቶቢስ አሽከርካሪ መቅጣቱን አስታወቀ

                    07/09/2017 ዓ.ም
                   **አዲስ አበባ**    

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በለገሀር አከባቢ የከተማ አውቶቢስ ሹፌር ከመኪናው የጠረገውን ደረቅ ቆሻሻን አስፓልት ላይ በመጣሉ በደንብ ቁጥር 167/2016 መሰረት አምስት ሺህ ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ማድረጉን አስታወቀ ። 

ድርጊቱን የፈጸመው ግለሰብ በጊዜው ተሸከርካሪዉን ይዞ ከቦታዉ ቢሰወርም በተደረገዉ ክትትል በዛሬዉ እለት የካ
 ክፍለ ከተማ  ወረዳ 6 ላይ ሹፈሩን ከነተሸከርካሪው በቁጥጥር ሰር በማዋል መንገድ በማቆሸሸ ለተላለፈዉ የደንብ ጥሰት የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል ። 

ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለሰጠው ጥቆማ ከልብ እያመሠገነ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች  መረጃ  በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ያቀርባል። 

መረጃው :- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments