
የደንብ ማስከበር ሰራተኞች ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ተገለፀ
የደንብ ማስከበር ሰራተኞች ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ተገለፀ
ሚያዚያ 17-2017ዓም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ለክፍለ ከተማው ሁሉም ወረዳዎች ለሚገኙ ከ650 በላይ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በስነምግባር እና ፀረ-ሙስና ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ደንብ ማስከበር ቅርንጯፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ደጀኔ ነገሮ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የደንብ ማስከበር ሰራተኞች በጥሩ ስነ-ምግባር ታንፀው የደንብ መተላለፎችን ለማስቀረት አያደረጉት ያለው ጥረት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ሰራተኞቹ የደንብ መተላለፎችን ከመከላከል ባለፈ በከተማዋ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ እዮብ ከበደ በበኩላቸው የዘርፉ ሰራተኞች ጥሩ ስነ-ምግባርን ተላብሰው ከፀረሙስና የፀዳ አገልግሎት በመስጠት ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ሀላፊነት በሙያዊ ስነ-ምግባር መፈፀም እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡
ሰልጣኞች በበኩላቸው ከብልሹ አሰራር የፀዳና ደንብና መመሪያ መሰረት ያደረገ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠናው ከፍተኛ አስተዎፅኦ እንዳለው ተናግረዋል::
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments