ባለስልጣኑ ያልተጣራ ፍሳሽ በመልቀቅ ወንዝን የበ...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ ያልተጣራ ፍሳሽ በመልቀቅ ወንዝን የበከሉ ሁለት ተቋማት እያንዳንዳቸው 1,000,000 ብር በመቅጣት እርምጃ መውሰዱን ገለፀ

ባለስልጣኑ ያልተጣራ ፍሳሽ በመልቀቅ ወንዝን የበከሉ ሁለት ተቋማት እያንዳንዳቸው 1,000,000 ብር በመቅጣት እርምጃ መውሰዱን ገለፀ

               24/07/2017 ዓ.ም
               ****አዲስ አበባ**** 

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር በልደታ ክ/ከተማ 2 ፍሳሽን ወደ ወንዝን በመልቀቅ ወንዝ የበከሉ ሁለት ተቋማት እያንዳንዳቸው 1,000,000 ብር በድምሩ 2,000,000/ሁለት ሚሊዮን ብር  በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን ገለፀ።

ባለስልጣኑ ቢጂ አይ ኢትዮጲያ እና ሞሀ የለስላሳ መጠጦች ማምረቻ ድርጅቶች የሚለቁት ፍሳሽ በተደረገለት የናሙና ምርመራ ወንዝን የሚበክል መሆኑን የተረጋገጠ ሲሆን በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

ወንዞችን ከብክለት የፀዱ ከማድረግ አንፃር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና  የአካባቢ ጥበቃ  ባለስልጣን በጋራ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎችን በስፋት እየሰጡ መሆኑ ገልፀዋል።

በግንዛቤው መሠረት ተቋማትና ግለሰቦች ከህገወጥ ተግባራቸው ሊቆጠቡ ባለመቻላቸው አስተዳደራዊ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን ተመላክቷል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።

ለተጨማሪ መረጃ፦
የሶሻል ሚዲያ ገፆቻችን ፎሎው፣ላይክ እና ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።

ዌብሳይት ገፃችን፦
https://www.aacea.gov.et/

የፌስ ቡክ ገፃችን፦
https://www.facebook.com/profile.php?id=100082525711518&mibextid

የቲክቶክ አካውንታችን
https://www.tiktok.com/@addisababacodeenforcemen

የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/codeenforcement

የዩቱብ ቻናላችን
https://youtube.com/@A.A.C.ACODEENFORCEMENT


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments