
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና-ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለ1446ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና-ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ ለ1446ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት
20/07/2017 ዓ.ም
****አዲስ አበባ****
ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446 ዒድ አል-ፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ ዒድ ሙባረክ!!!
የኢድ-አልፈጥር በዓል የሰላም ፣የጤና ፣ የደስታ ፣ የፍቅር እና የመረዳዳት በዓል እንደሆንልን እመኛለሁ።
በዓሉን ስናከብር ህዝበ ሙስሊሙ በጾም ወቅት በአብሮነት፣በመተሳሰብ እና የተቸገሩ ወገኖች ማዕድ በማጋራት ያለውን በማካፈል ጾሙን ሲያስፈጥር እንደነበረ ሁሉ በበዓሉ እለት እና ከበዓል በኃላ ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ።
በበዓሉ እለትም የተቸገሩ ወገኖቻችንን በመርዳት፣ በመተዛዘን ካለን በማካፈል በዓሉን በአብሮነት ልናከብር ይገባል ።
ባለስልጣኑ በከተማዋ የሚስተዋለውን የደንብ ጥሰትና ህገ-ወጥነትን ለመከላከልና በሚያደርገው ጥረት ላይ ህብረተሰቡ የበኩሉን እንዲወጣ በዚህ አጋጣሚ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ።
ኢድ-ሙባርክ
ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments