ባለስልጣኑ መጪው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ መጪው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ውይይት አካሄደ ።

ባለስልጣኑ መጪው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ውይይት አካሄደ ። 

                19-07 -2017 ዓ.ም
                  **አዲስ አበባ** 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን በቀጣይ የሚከበረውን የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም ተከብሮ እንዲጠነቀቅ የባለስልጣኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከክ/ከተማ የደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል። 

በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ሻለቃ ዘሪሁን ተፈራ በዓሉን አስመልክቶ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የፀጥታ፣የህገወጥ እርዶችንና ሌሎች የደንብ መተላለፎች እንዳይከሰቱ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

አክለውም በዓሉ በሚከበርበት ወቅት በከተማዋ ላይ የተሰሩትን የኮሪደር መሠሰተ ልማቶች እንዳይበላሹ ህብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ከደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ጋር በመቀናጀት ከተማችንን ጽዱ እና ውብ እንድትሆን መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል ። 

ለውይይት መነሻ የተዘጋጀው ሰነድ የባለስልጣኑ የደንብ መተላለፍ ክትትል ፣ቁጥጥር እና እርምጃ አወሳሰድ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ግሩም ወ/መስቀል አቅርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዷል ። 

በመድረኩ በዓሉ ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅና በበዓሉን አስመልክቶ አላሰፈላጊ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖርና የግባእት እጥረት እንዳያጋጥም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት መስራት እንደሚያስፈልግ መልዕክት አስተላልፈዋል ። 

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን  ዳሬክቶሬት ነው፡፡


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments