
ባለስልጣኑ በትላንትና በዛሬው እለት ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
ባለስልጣኑ በትላንትና በዛሬው እለት ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
16/07/2017 ዓ.ም
****አዲስ አበባ****
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት በድምሩ 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ በየካ ክ/ከተማ 2,350,000 ብር፤ በቦሌ ክ/ከተማ 950,000 ብር ፤ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 1,050,000
ብር፤በቦሌ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 600,000
ብር ቅጣት ተቀጥቷል።
በተያያዘ ዜና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 370,000 ብር ፤በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 300,000 ብር እና በኮልፌ ክፍለ ከተማ 50,000 ብር ቅጣት በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል፡፡
ባለስልጣኑ በሁለት ቀናት በአጠቃላይ 14 ድርጅቶች እና 14 ግለሰቦች በድምሩ 5,670,000/ አምስት ሚሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሺህ/ ብር ቅጣት በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።
ባለስልጣኑ ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ እንዳይበከሉ ለድርጅቶችና ለግለሰቦች በደንብ ቁጥር 180/2017 ላይ ሰፊ የግንዛቤ ስራ መስራቱ የገለጸ ሲሆን በቀጣይ የግንዛቤና ህግ የማስከበሩ ስራ አጠናክሮ አንደሚቀጥል አስታውቋል።
መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments