ባለስልጣኑ ወንዝን በመበከል ከድርጊታቸው ያልተቆ...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ ወንዝን በመበከል ከድርጊታቸው ያልተቆጠቡ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን 5,910,000/ አምስት ሚሊየን ዘጠኝ መቶ አስር ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ

ባለስልጣኑ ወንዝን በመበከል ከድርጊታቸው ያልተቆጠቡ ድርጅቶች እና ግለሰቦችን 5,910,000/ አምስት ሚሊየን ዘጠኝ መቶ አስር ሺህ/ ብር መቅጣቱ አስታወቀ
        
           10/07/2017 ዓ.ም
         ****አዲስ አበባ****

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣ ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር  ወንዞችና የወንዞች ዳርቻ የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦችን  በዛሬው እለትም በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት  5,910,000/ አምስት ሚሊየን ዘጠኝ መቶ አስር ሺህ/ ብር የገንዘብ ቅጣት  በመቅጣት  አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ 2,100,000 ብር፤በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ 910,000 ብር ፤ በኮልፌ ክፍለ ከተማ 690,000 ብር፤በየካ ክ/ከተማ 600,000 ብር ቅጣት ቀጥቷል።

በያያዘ ዜና በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር ፤በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር እና በልደታ ክ/ከተማ 400,000 ብር በመቅጣት ለመንግስት ገቢ ተደርጓል።

በአጠቃላይ በዛሬው እለት 17 ድርጅት እና
8 ግለሰቦች በድምሩ 5,910,000/ አምስት ሚሊየን ዘጠኝ መቶ አስር ሺህ/ብር  በመቅጣት  አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።

ባለስልጣኑ በተሰጠው ግንዛቤ መሠረት ወንወዞችና የወንዞች ዳርቻ በመበከል ከድርጊታቸው ያልተቆጠቡ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ  አንደሚቀጥል አስታውቋል።

መረጃው:- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ኮሙኔኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው።


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments