
ባለስልጣኑ የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ
ባለስልጣኑ የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ
08-07 -2017 ዓ.ም
**አዲስ አበባ**
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ባደረገው ጠንካራ ክትትል መሠረት የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ ።
በአራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መዝገቡ ዲማ እንደገለፁት በግለሰብ ግቢ ውስጥ መሸሸጊያ በማድረግ ተከማችተው የተቀመጡ በርካታ ህገወጥ የንግድ እቃዎችን በደንብ ማስከበር ፅ/ቤት በግብረሀይል በመውረስ በግምት ከ400,000/ አራት መቶ ሺህ/ ብር በላይ የሚገመቱ እቃዎቾ ለመንግስት ገቢ ተደርጓል ።
ባለስልጣኑ ህገወጥነትን እደማይታገስና በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንደሚገባቸውና ወደ ህጋዊ መንገድ እንዲገቡ አሳስቧል ።
ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡
Comments
Nothing was found.
Leave Your Comments