ባለስልጣኑ የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠ...

image description
- In code inforcement    0

ባለስልጣኑ የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ

ባለስልጣኑ የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ 

                  08-07 -2017 ዓ.ም
                  **አዲስ አበባ** 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር የደንብ ማስከበር ባለስልጣን በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤቱ ባደረገው ጠንካራ ክትትል መሠረት የህገ-ወጥ ነጋዴዎች መጋዘን በመቆጣጠር ከነ ሙሉ እቃው እርምጃ መውሰዱን ገለፀ ። 

በአራዳ ክፍለ ከተማ የወረዳ 05 ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መዝገቡ ዲማ  እንደገለፁት በግለሰብ ግቢ ውስጥ መሸሸጊያ በማድረግ ተከማችተው የተቀመጡ  በርካታ ህገወጥ የንግድ እቃዎችን በደንብ ማስከበር ፅ/ቤት  በግብረሀይል በመውረስ በግምት ከ400,000/ አራት መቶ ሺህ/ ብር በላይ የሚገመቱ እቃዎቾ ለመንግስት ገቢ ተደርጓል ። 

ባለስልጣኑ ህገወጥነትን እደማይታገስና በዚህ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ከድርጊታቸው መቆጠብ እንደሚገባቸውና ወደ ህጋዊ መንገድ እንዲገቡ አሳስቧል ። 

ዘገበው ፡-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ኮሙዩኒኬሽን ዳሬክቶሬት ነው፡፡


Comments

Nothing was found.

Leave Your Comments